መሬት፣ መሬት፣ ሁለት

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

መሬት ማለት ብዙ ነገር ነው፤ ገበሬው መሬት ሲል ለም አፈር ነው፤ ለከብት አርቢው የግጦሽ መሬት ነው፤ መሀንዲሱ መሬት ሲል ደልዳላ ሜዳ፣ ድንጋይና አሸዋ ነው፤ ስለመሬት ስናስብ በግድ ስለዓየር ጠባዩና ስለውሃም እናስባለን፤ ለደላላውና ለኪራይ ሰብሳቢው መሬት ሸቀጥ ነው፤ የመሬቱ መሸጥ የሚጎዳው በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ተከታታይ ትውልዶችን ነው፤ ገንዘባቸውን ይዘው ወደሌላ አገር የሚንሸራተቱትን አይደለም፡፡

ኢትዮጵያ ነዳጅ ዘይት ወይም ሌላ ማዕድን ስለሌላት ከቡናና ከቆዳ የበለጠ ገቢ ያስገኛል ተብሎ የተገመተው መሬት ነው፣ መሬትን በመሸጥ ወይም እያከራዩ ኪራይ በመሰብሰብ በመበልጸግ ይቻላል ተብሎ ታስቦአል፤ ለውጭ አገር ሰዎች በማናቸውም መንገድ የመሬት መብትን ማስተላለፍ ውሎ አድሮ አብዛኛውን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያደኸይ እንደሚሆን አያጠራጥርም፤ ጥቂት ሰዎች በጣም እንደሚከብሩም አይጠረጠርም፡፡

ወድቆ በተነሳው ባንዲራ! አትቀልዱብን!!

ተመስገን ደሳለኝ
የሆነ ሆኖ አንድ አዋጅ ከታወጀ በኋላ ‹‹አዋጁ አስፈላጊ ነው ወይስ አያስፈልግም?›› በሚል የሚዘጋጁት የውይይት መድረኮች ህዝብ በመንግስት ላይ ያለው ቁጣ እና ጥላቻ እንዲጨምር ከማድረግ ውጪ አንዳችም ፋይዳ የለውም፡፡ ምክንያቱም ሲጀመር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ፀደቀ የተባለ አዋጅ እንደገና ተመልሶ ወደ ህዝብ መውረዱ አስፈላጊነቱ ለማንም ግልፅ አይደለም፡፡ አሊያም በተወካዮች ምክር ቤት የሚሰማው የአንድ ፓርቲ ድምፅ ነው፣ የህዝቡ ቅሬታ አይቀርብም፣ የሀሳብ ፍጭት የለም ብላችሁ ልክ አንደኛ እንደተራው ዜጋ የምታምኑ ከሆነ፣ ሁለት አማራጮች አሏችሁ፡፡ የመጀመሪያውና ጠቃሚው አማራጭ ፓርላማውን በትኖ፣ አዲስ ፓርላማ በምርጫ ማቋቋም ነው፡፡ ይሄን ከመረጣችሁ ወዲህም ታሪክ ታሰራላችሁ፡፡ ሁለተኛው ምርጫ ግን ምንም አይነት አዋጅና ህግ በፓርላማ ቀርቦ ከመፅደቁ በፊት እንደ አቴናውያን የየከተማውን ህዝብ በየአደባባዩ ሰብስቦ ማወያየት ነው፡፡ ይሄ ለቀልዱም ይመቻችል፡፡

ኢህአዴግ ሲቪል ወይስ ወታደራዊ?

በሙሉነህ አያሌው
ከየትኛውም ጊዜ በበለጠ ብዙ ህጐች አሁንም ወጥተዋል፡፡ ህገ- መንግስቱም ቢሆን ከአንዳንድ ለትርጉም ከተጋለጡ አንቀፆች ውጭ ምንም የሚወጣለት አይደለም፡፡ ችግሩ ህጉ ተግባር ላይ ሲወርድ፣ አስፈፃሚው በፍርድ ቤቶች ላይ ያለው ተፅዕኖ ቀጥተኛ መሆኑ ነው፡፡ ከህጉ ይልቅ የበላይ የሆነ ግለሰብ እንዳለ በግልፅ መመልከት እንችላለን፡፡ ፍርድ ቤቶቹ ይለቋቸው ይሆን? ከማለት ይልቅ ‹‹ሰውየው›› ምህረት ያደርጉላቸው ይሆን? ማለትን እናስቀድማለን፡፡ መንግስቱም እኮ ይሄው ነበር፡፡ እንዲህም ያደርግ ነበር፡፡

‹‹ሀገር በእጃችን…››

የሆነ ሆኖ ‹‹ሀገር በእጃችን›› የሚለው አማርኛ ዛሬ የለም፡፡ ‹‹ሀገር በእጄ›› በሚለው ተቀይሮአልና፡፡ የሁሉ ነገር አድራጊ ፈጣሪ አንድ እሳቸው ናቸው፡፡ ለምሳሌ መንግስታቸውን የሚያስተች እና የሚያስነቅፍ ውሳኔ ወይም እቅድ ተተግብሮ ከተገኘ ‹‹ፓርቲው የወሰነው›› እንደሆነ ይነግሩሀል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ውሳኔው በብዙ ህዝብ የሚደገፍ ከሆነ ጆሮህ እስኪደነቁር፣ ልብ ቀጥ እስክትል ‹‹አባይን የደፈረ መሪ›› የሚል መፈክር ትሰማለህ፡፡

ይድረስ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሰላይዎችዎን ይሰብስቡልን!

በተመስገን ደሳለኝ

ክቡር አቶ መለስ ዜናዊ የኤፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር፡- በተደጋጋሚ ጊዜ ቅሬታዬን እንደጻፍኩልዎ ይታወቃል፡፡ በተደጋጋሚ ጊዜም ስልጣንዎን ይለቁ ዘንድ ተማፅኝዎታለሁ፡፡ በተደጋጋሚ ጊዜም አምባገነናዊ አስተዳደርዎን ነቅፌአለሁ፡፡ በተደጋጋሚ ጊዜም የሀገሪቱን ፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ጠቅልለው መያዝዎን፣ ለሀገራችን የማይበጅ ስለመሆኑ ምክንያታዊ ትችት ፅፌአለሁ፡፡ በተደጋጋሚ ጊዜም…
ታዲያ ይህን ሁሉ ደፍሬ ስፅፍልዎ በማንም ተመክቼ አይደለም፡፡ አስተዳደርዎ ዴሞክራሲያዊ ሆኖም ‹‹የሚነካኝ የለም›› በሚል መንፈስም አይደለም፡፡ እንዲህማ ልል አልችልም፡፡ ከእኔ በፊት በዚህ መልኩ ይተችዎት የነበሩ ጋዜጠኞችን እንዴት ከጨዋታ ውጪ እንዳደረጓቸው የአደባባይ ሚስጥር ነውና፡፡ ከሌላው ኢትዮጵያዊም የተለየ ደፋር ሆኜም አይደለም፡፡ እርዳታ እና ብድር ሰጪ ሀገራትንም ተማምኜ አይደለም፡፡ ይመኑኝም አይመኑኝም ስራዬን እየሰራሁ ያለሁት የሀገሬን ህገ-መንግስት ተማምኜ እንደሆነና እርስዎም ከእለታት አንድቀን ህገ-መንግስቱን ያከብራሉ በሚል ተስፋ እንደሆነ ደግሜ ደጋግሜ የነፍሴን ያህል በምወዳት (በአድዋ ድል ላይ በተውለበለበችው) ባንዲራ ስም እነግርዎታለሁ፡፡

የአቶ በረከት የ40 አመት መርገም

ካሳሁን ይልማ

የአዲስ ነገር ባልደረባ

ሽመልስ ከማል ጋዜጠኞችን እና የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን ሽብርተኞች ሲያደርጓቸው በቅርቡ ከኬንያ ጋራ በአልሻባብ ጉዳይ እሰጥ-አገባ ውስጥ የገባቸውን ኤርትራን አያይዘው አንስተዋል:: የአልሻባብ አጋር ተብላ ከምትጠረጠረዋ እና የዩኤን.ኤች.ሲ.አር ማዕቀብ ሰለባ ከሆነችው ኤርትራ ጋራ ጋዜጠኞች እና የፓርቲ አመራሮቹን ግንኙነት አላቸው መባሉ አሸባሪነታቸውን ያጎላዋል:: ምክንያቱም የገዢው መንግስት ወዳጅ ሀገሮች “ሽብርተኛ” የሚለው ቃል ሳይቀር ስለሚያስበረግጋቸው የአቶ ሽመልስ ማብራርያ ዋይት ሐውስ ሰተት ብሎ ለመግባት የረቀቀ የፍተሻ ጊዜ አይወስድበትም:: በብሮድካስቲንግ ፕሮፖጋንዳ ቀመር::
ኢሕአዴግ “የሲኒዋን ማዕበል” ድምር ውጤት የማስላት ስህተት በፈጸመበት የ97 ምርጫ ማግስት ሕገ መንግስት ንደዋል ያላቸውን የቅንጅት አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ የሲቪል ማኅበራት ሠራተኞች እና ከተቃዋሚ ፓርቲ ጎራ ተሰልፈዋል ያላቸውን ግለሰቦች በየእስር ቤቱ በማጎር የቤት ሥራውን ከጀመረ ወዲህ አላንቀላፋም::

ዜና /ሲዊዲናዊያን ጋዜጠኞች ላይ የ 11 ዓመት እስራት የተፈረደባቸው እነ ርዕዮት ዓለሙ ለጥር 1 ቀን 2004 ዓ.ም ተቀጠሩ/

ሲዊዲናዊያን ጋዜጠኞች ላይ የ 11 ዓመት እስራት የተፈረደባቸው እነ ርዕዮት ዓለሙ ለጥር 1 ቀን 2004 ዓ.ም ተቀጠሩ
ዛሬ ማክሰኞ ታኅሣሥ 17 ቀን 2004ዓ.ም በዋለው ችሎት “በሕገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ በመግባትና የጋዜጠኝነት ሙያን እንደ ሽፋን በመጠቀም ለሽብርተኝነት ድጋፍ በመስጠት” ወንጀል የተከሰሱት ሁለቱ ሲዊዲናዊያን ጋዜጠኞች ላይ የ 11 ዓመት እስራት የተፈረደባቸው ሲሆን የሲዊዲን አምባሳደርም ችሎቱን ረግጠው እንደወጡ ሪፖርተራችን ዘግቧል፡፡
በተያያዘ ዜና የነ ርዕዮት ዓለሙን ክስ ሲያይ የነበረው ችሎት ውሳኔ ለመስጠት ለጥር 1 ቀን 2004 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቶ ችሎቱ ተበትኗል፡፡

የሁለቱ ‹‹ኢህአፓ››ዎች ጉራማይሌ ወግ (በረከት ስምኦን እና ብርሃኑ ነጋ)

በተመስገን ደሳለኝ
ኢህዴንም በእነበረከት አጋፋሪነት ተመሰረተ፡፡ ከድል በኋላ ደግሞ ኢህዴን ወደ ብአዴን በደብተራ ጥበብ፣ ጠበበ፡፡ እነሆም ብአዴን ከሌሎች ሶስት ብሄር ተኮር ድርጅቶች ጋር ተጋግዞ ሀገር ማስተዳደር ከጀመረ ዘንድሮ 21ኛ አመቱን ይዟል፡፡ ማን ያውቃል? እኛም እንዲሁ እንደተበሳጨን፤ እነሱም እንዲሁ እያሾፉ 42ኛ አመታቸውንም ሊያከብሩ ይችላሉ፡፡ በእርግጥ ይሄ ግምት ነው፡፡ ከግምት ስንመለስ ግን ቀጥለን የምናየውን ርዕስ እናገኛለን፡፡

Pages